• Home
  • News
    • Press Release
    • Press Conference
  • Event
  • Complaint Information
  • Videos
  • About
    • Members
    • Gallery
  • Contact
ETHIOPIAN RC
  • Home
  • News
    • Press Release
    • Press Conference
  • Event
  • Complaint Information
  • Videos
  • About
    • Members
    • Gallery
  • Contact

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከዕርቀ ሰላም ኮሚሽን ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 'የዕርቅ ሀሳብ አለኝ' ፕሮግራም የዕወቅናና የማበረታቻ ፕሮግራም በካፒታል ሆቴል ተካሂዷል

9/21/2020

Comments

 
Picture
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከዕርቀ ሰላም ኮሚሽን ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 'የዕርቅ ሀሳብ አለኝ' መርኃግብር ፕሮግራም የዕወቅናና የማበረታቻ ፕሮግራም ዛሬ በካፒታል ሆቴል ተካሂዷል።

በመርኃግብሩ በተሳታፊዎች ከተሰሩ ሥራዎች መካከል 7 የሚሆን የተለያዩ የሥራዎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል። ገዲዝም የተሰኘ ከተሳታፊዎች የተገኘ አንድ ጹሑፍ ላይ መሰረት ያደረገ በአኒሜሽን የተሰራ ትዕይንትም ለዕይታ ቀርቧል።
የዕርቀ ሰላም ኮሚሽን ሰብሳቢ ብጹዕ ካርዲናል ብርሃነ ኢየሱስን ጨምሮ በመድረኩ የተገኙ እንግዶች ለተሳታፊ ወጣቶች መልዕክትና ምሥጋናቸውን አቅርበዋል። 
በዕለቱ ጭውውቶች አነቃቂ ንግግሮችና የመዝናኛ ሥራዎች የቀረቡ ሲሆን በፕሮግራሙ መጨረሻ ላይ በአቀራረባቸው አሸናፊ ለሆኑ ለግልና የቡድን ተሳታፊዎች ሽልማቶች ተሰጥተዋል። 

​የተሸለሙ አሸናፊዎች ጥቂቶች ቢሆኑም እንደ ሥራቸውና እንደ ጥረታቸው ሁሉም ሥራዎች (ከ360 በላይ ጹሑፎች) አሸናፊዎች ናቸው። በቀጣይም በዛሬው ዝግጅት ብቻ ይህ ተሳትፎ እንዳይቆምና እንዲቀጥል በመግባባት ላይ ተደርሶ የዝግጅቱ ፍጻሜ ሆኗል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከዕርቀ ሰላም ኮሚሽን ጋር በትብብር ይህንን ዝግጅት ሲያዘጋጅ ወጣቶች እድል ቢያገኙ ትልቅ አበርክቶ እንዳላቸው እንዲሁም እውቀትና ጉልበታቸውን ተጠቅመው በዕርቅ ውስጥ መሳተፍ እንደሚችሉ ማሳያ ይሆን ዘንድ ነው። 

ይሄንንም ፕሮጀክት ጨምሮ በወጣቶች ዙሪያ የምንሰራቸውን ስራዎች ወደፊትም አጠንክረን የምንቀጥል ይሆናል። ረጅም ርቀት አቋርጣችሁ ከተለያዩ አከባቢዎች የተገኛችሁ እንዲሁም ይህ ሥራ ዕውን እንዲሆን ለደከማችሁ የዕርቀ ሰላም ኮሚሽን አባላትና ሰራተኞች በሙሉ ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን።
Comments

    Archives

    November 2020
    October 2020
    September 2020
    August 2020
    July 2020
    June 2020
    May 2020
    March 2020
    February 2020
    September 2019

    Categories

    All
    News

    RSS Feed

Picture
                          Social Media
                              Facebook : ERC
​
                              
Twitter : ERC

        © 2020 Ethiopian Reconciliation Commission​​
  • Home
  • News
    • Press Release
    • Press Conference
  • Event
  • Complaint Information
  • Videos
  • About
    • Members
    • Gallery
  • Contact