• Home
  • News
    • Press Release
    • Press Conference
  • Event
  • Complaint Information
  • Videos
  • About
    • Members
    • Gallery
  • Contact
ETHIOPIAN RC
  • Home
  • News
    • Press Release
    • Press Conference
  • Event
  • Complaint Information
  • Videos
  • About
    • Members
    • Gallery
  • Contact

በወቅታዊ ሁኔታ ላይ ከእርቀ ሰላም ኮሚሽን የተሰጠ መግለጫ

11/5/2020

Comments

 
Picture
​የኢትዮጵያ እርቀ ሰላም ኮሚሽን የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ በአገሪቱ እየተከሰቱ ያሉ ዘርን ማእከል ያደረጉ ተደጋጋሚ ጥቃቶች መኖራቸውን ተወያይቷል። በምእራብ ወለጋ ጉሊሶ ወረዳ ጋዋ ጋንቃ ቀበሌ፣ በጉራፈርዳ እና በመተከል ዞን ምንም በማያቁና ምንም አይነት የፖለቲካ ግንኙነትና እንቅስቃሴ በሌላቸው ንፁሃን ዜጎች ላይ የደረሰው ዘግናኝ ግድያ በእጅጉ አሳዛኝና የሚያስቆጣ ሆኖ አግኝቶታል።
ይህ አንድን ዘር ማእከል አድርጎ የተፈፀመ የጅምላ ግድያ ከመሆኑም በላይ ኢሰብአዊ ድርጊት በመሆኑ ኮሚሽኑ ድርጊቱን ያወግዛል። መንግስት ይህን ድርጊት በፈፀሙ ቡድኖች ላይ አስቸኳይ እርምጃ በመውሰድ አጥፊዎቹን ለፍርድ እንዲቀርብ ኮሚሽኑ አጥብቆ ይጠይቃል።
 
ከግድያው ጋር በተያያዘ ባደረባቸው ስጋትና ፍርሃት ከቀያቸው ለተፈናቀሉ ወገኖች ዋስትና በመስጠት መልሰው እንዲቋቋሙ መንግስትና የሚመለከታቸው አካላት ድጋፍ እንዲያደርጉ እንጠይቃለን። እንዲህ አይነት ዘግናኝ ወንጀሎችን የሚፈፅሙ ቡድኖችም ንፁሃን ዜጎችን ለፖለቲካ ቁማር ለማዋል ሲባል ኢ ሰብአዊ ድርጊት ከመፈፀም ተቆጥበው በሰላም በመግባባትና በድርድር የሚንቀሳቀሱበትን ሁኔታ ማሰብ እንዳለባቸው እናስገነዝባለን።
 
ምንም በማያውቁት ሁኔታ በጅምላ የተገደሉ ንፁሃን ዜጎችን ፈጣሪ ነፍሳቸውን እንዲምር በመማፀን ለቤተሰቦቻቸው መፅናናትን እንመኛለን።
Comments

    Archives

    November 2020
    October 2020
    September 2020
    August 2020
    July 2020
    June 2020
    May 2020
    March 2020
    February 2020
    September 2019

    Categories

    All
    News

    RSS Feed

Picture
                          Social Media
                              Facebook : ERC
​
                              
Twitter : ERC

        © 2020 Ethiopian Reconciliation Commission​​
  • Home
  • News
    • Press Release
    • Press Conference
  • Event
  • Complaint Information
  • Videos
  • About
    • Members
    • Gallery
  • Contact