• Home
  • News
    • Press Release
    • Press Conference
  • Event
  • Complaint Information
  • Videos
  • About
    • Members
    • Gallery
  • Contact
ETHIOPIAN RC
  • Home
  • News
    • Press Release
    • Press Conference
  • Event
  • Complaint Information
  • Videos
  • About
    • Members
    • Gallery
  • Contact

የአስታራቂ እናቶች ተሞክሯቸውን ለእርቀ ሰላም ኮሚሽን አቀረቡ::

5/22/2020

Comments

 
Picture
​በአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር ጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 ቀጨኔ አካባቢ የሚኖሩ አስታራቂ እናቶች በእራስ ተነሳሽነት በተለያዩ ምክንያቶች የተጋጩ የአካባቢው ነዋሪዎችን ማስታረቃቸው ለዕርቀ ሰላም ኮሚሽን ገለፁ፡፡
 
ቁጥራቸው አምስት በጎ ፈቃደኛ እናቶች በአካባቢው ለዘመናት በህብረተሰብ ውስጥ የነበሩ ግጭቶች አለመግባባቶችና ቂምና ጥላቻን ለማስወገድ እየሰሩ መሆኑ አብራርተዋል፡፡ እናቶች ግጭቶች ከህግ በፊት በአካባቢ ሽማግሌዎች መፍታት ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን በመረዳት ለበርካታ ዓመታት በቂም ጥላቻ እና ግጭት ውስጥ የነበሩ 250 የአካባቢው ሰዎች ይቅር በማባባል በሰላም እንዲኖሩ አስችለዋል፡፡
 
የእርቅ ሂደቱ  የአካባቢውን ባህልና እምነት መሰረት በማድረግ  ‹‹ይቅር ማለት ለፈጣሪ ነው፤ ይቅር ባይነትም ታላቅነት ነው ›› በማለት የተጋጩ ግለሰቦች፣ ቤተሰቦች እና ድንበርተኞችን ይቅር እንዲባባሉና በሰላም እንኖሩ ማስቻላቸውን አብራርተዋል፡፡
 
ከተቋቋሙ ሁለት ወራት የስቆጠሩት እነኚህ በጎ ፈቃደኛ አስታራቂ እናቶች በማህበረሰቡ ውስጥ ያላቸውን ተቀባይነትና ተምሳሌታዊነት በመጠቀም እስካሁን የአካሄዷቸው የይቅርታና የማስታረቅ ስራዎቻቸውን ወደፊትም አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልፀዋል፡፡
 
የእርቀ ሰላም ኮሚሽን አባል የሆኑት የጥበብ ሰው ደበበ እሸቱ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት እንዲህ ያለው የአስታራቂ እናቶች ማህበረሰብ ተኮር ይቅርታና የእርቅ ስነስርአት በእጅጉ የሚደነቅና የሚበረታታ በመሆኑ እናቶች እያደረጉ ያሉት ወደ ሌሎች አካባቢዎች  ቢሸጋገር ሀገራዊ ጠቀሜታው የጎላ ነው ብለዋል፡፡
Comments

“እኔም የዕርቅ ሀሳብ አለኝ “ የሚል ወጣቱን አሳታፊ የሚያደርግ ፕሮጀክት ይፋ ሆነ፡፡

5/21/2020

Comments

 
Picture

የዕርቀ ሠላም ኮሚሽን ሕብረተሰቡ በዕርቅና በሠላም ጉዳይ ላይ ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርግ የተለያዩ ዕቅዶችን ነድፎ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል፡፡ ይህንን ዕቅድ ተግባራዊ ለማድረግ ‘ቲክቫህ ኢትዮጲያ’  ከሚባል የቴሌ ግራም ቻናል ጋር በመተባበር ወጣቱን አሳታፊ የሆነ ፕሮጀክት ይፋ አድርገዋል፡፡ በርካታ ተከታዮች ያሉት ቻናሉ ወጣቱ በተለያዩ መስክ ያለውን እምቅ ችሎታ ተጠቀሞ  በየአካባቢያቸዉ ያለዉን ሰላምንና ዕርቅን ማስፈን ሚችሉ ሀገር በቀል እዉቀቶችንና የዕርቅ አፈታት ስርዓቶችን  እንዲለዩና ለሌላዉ ማህበረሰብ ክፍል እንዲያሳዉቁ የሚያስችል ነዉ፡፡ 
የገፁ አስተባባሪ ወጣት በረከት ጉዲሳ እንደተናገረዉ ወጣቱ የተለያዩ የመረጃ አሰባሰብ ዘዴዎችን ተጠቅሞ በየአካባቢያቸዉ ያለዉን የዕርቀ ሠላም ሀሳቦችን በተቀመጠባቸዉ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ማስረከብ ይኖርባቸዋል፡፡
 
ፕሮጀክቱን በይፋ ያስጀመሩት የዕርቀ ሰላም ኮሚሽን ሰብሳቢ ካርዲናል ብርሃነ እየሱስ ሱራፌል ይህ ‘ቲክቫህ ኢትዮጲያ’ አስተባባሪ ወጣቶች የያዙት ሀሳብ ከዕርቀ ሠላም ኮሚሽን ተልዕኮ ጋር በእጅጉ የሚገናኝ ስለሆነ ኮሚሽኑ ወጣቱን የሕብረተሰብ ክፍል ለሰብዓዊ አገልግሎትና ለእርቀ ሰላም ለማነሳሳት ከዚህ  ማህበራዊ ሚዲያ ጋር መስራት ጥሩ አማራጭ ነዉ ብለዋል፡፡
​
ወጣቱ ምንም እንኳ በሚከሰቱ ግጭቶች ቀዳሚ  ተሳታፊና ቀዳሚ ተጎጂ ቢሆንም የሰላም ግንባታ ዉስጥ ተሳታፊ እንዲሆን የሚደረገዉ እንቅስቃሴ ክፍተኛ የሚባል አይደለም፡፡  እንዲሁም በአካባቢዉ ያሉትን አገር በቀል የሠላም  እሴቶች እና የዕርቅ ስርአቱን የሰላም እንዲያዉቁ ሲደረግ አይስተዋልም፡፡ ክዚህ ባሻገር ወጣቱ የዕርቅና የሰላም እሴቶች እንዲተገብራቸዉና እንዲያዉቃቸዉ የሚስችል መደላደል አልተነደፈለትም፡፡  ይህ ከቲከቫህ የሚደረግ ፕሮጀክት እነዚህን በማህበረሰቡ ወስጥ የሚገኙ የዕርቅ ስርአቶች ወጣቱ እንዲመረምር እንዲያዉቅና በመረጃ የተደገፈ ጥናት እንዲያደርግ ያስችላል፡፡

Comments

መተሳሰብ ላይ መሠረት ያደረገ ድጋፍ

5/18/2020

Comments

 
Picture
“ወጣት ለወጣት ትስስር” በሚል መሪ ቃል የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል በአዲስ አበባ ወጣት በጎ ፊቃደኞች አስተባባሪነት እና በዕረቀ ሠላም ኮሚሽን ድጋፍ ለኦሎንኮሚ እና አምቦ ከተማ ነዋሪዎች የምግብና የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁስ ተበረከተ፡፡

የመርሃ ግብሩ ዋና አላማ ወጣቶች ያላቸዉን ንፁህ ሂሊና ለበጎ ተገግባር እንዲጠቀሙበት እና እንዲህ ባለ አስክፊና አስፈሪ ጊዜ ሰዎች በፍቅር፣ በሰላም እና በመተጋጋዝ ማሰላፍ እነድችሉ ነዉ፡፡

ወጣቶቹ ከአዲስ አበባ ሲነሱ ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነእየሱ፣ የዕርቀ ሠላም ኮሚሽን ሰበሳቢ አሸኛኘት ያደረጉላቸዉ ሲሆን ይህ በጎ ተግባር ወጣቱ ከመጋጨት ይልቅ መተሳሰብን፤ ከመራራቅ ይልቅ መቀራረብን፤ የእኔ ከማለት የሁላችን ማለትን፤ ከልዩነት ይልቅ  አንድነትን እና መተሳሰብን ያመጣል ብለዋል፡፡ እነደዚህ አይነት የበጎ ፊቃደኞች ተነሳሽነት በአገራችን የሚገኙ ብሔሮች ከሚያራርቃችዉ የሚያቀራርባቸዉ፤ ከሚያጣላቸዉ ይልቅ የሚያስማማቸዉ፤ ከሚያለያያቸዉ ይልቅ የሚያመሳስላቸዉ እነደሚበልጥ ለማመለላከትም ጭምር ነዉ፡፡   

ይህን መሰል ዝግጅት በለሎች አካባቢዎች ቢቀጥል መተሳሰቡና መልካም ግንኙነቱ ይበልጥ እነድሚያጠነክረዉ ጠቁመዋል፡፡
​
29/08/2012 አ.ም
​https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=2566546366897178&id=1511591522392673
Comments

    Archives

    February 2021
    November 2020
    October 2020
    September 2020
    August 2020
    July 2020
    June 2020
    May 2020
    March 2020
    February 2020
    September 2019

    Categories

    All
    News

    RSS Feed

Picture
                          Social Media
                              Facebook : ERC
​
                              
Twitter : ERC

        © 2020 Ethiopian Reconciliation Commission​​
  • Home
  • News
    • Press Release
    • Press Conference
  • Event
  • Complaint Information
  • Videos
  • About
    • Members
    • Gallery
  • Contact