• Home
  • News
    • Press Release
    • Press Conference
  • Event
  • Complaint Information
  • Videos
  • About
    • Members
    • Gallery
  • Contact
ETHIOPIAN RC
  • Home
  • News
    • Press Release
    • Press Conference
  • Event
  • Complaint Information
  • Videos
  • About
    • Members
    • Gallery
  • Contact

በእርቀ ሰላም ኮሚሽን በተጓደሉ አባላት ምትክ አዳዲስ የኮሚሽን አባላት ሹመት፡፡

6/25/2020

Comments

 
Picture
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰኔ 18/2012 ዓ.ም ባካሄደው ስብሰባ በእርቀ ሰላም ኮሚሽን በተጓደሉ አባላት ምትክ አምስት የኮሚሽን አባላትን ሾሟል፡፡ እነዚህም፡-
  1. ሬቨናንድ ደረጀ ጀምበሩ ካሳ
  2. አቶ ደመላሽ ያደቴ ተፈራ
  3. ዶ/ር ዕዝራ አባተ ይማም
  4. ወ/ሮ ፋጡማ ሀቴ ሃፊ
  5. ጋራድ ኩልሜ መሃመድ ዶል
በአንድ ተቃውሞ እና በአንድ ድምፅ ታዕቅቦ በአብላጫ ድምፅ እንዲሾሙ አጽድቋል፡፡ ተሿሚዎቹም በፓርላማው ፊት ቀርበው የተጣለባቸውን ኃላፊነት በአግባቡ እና በኃላፊነት ለመወጣት ቃለመሃላ ፈጽመዋል፡፡
የእርቀ ሰላም ኮሚሽን በ41 የኮሚሽን አባላት የሚመራ እና በህዝቦች መካከል በእውነትና ፍትህ ላይ የተመሰረተ ዕርቅ እንዲሰፍን የሚሰራ በአዋጅ ቁጥር 1102/2011 የተመሰረተ ተቋም ነው፡፡ 
Comments

የእርቀ ሠላም ኮሚሽን አባላት በአረንጓዴ አሻራ መረሃ ግብር ላይ ያደረጉትን ተሳትፎ የሚያሳይ በኢትዮጰያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የቀረበ ሪፖርት

6/23/2020

Comments

 
Comments

የአረንጓዴ አሻራ ስኬት በዕርቀ ሠላም ኮሚሽን አባላት::

6/19/2020

Comments

 
Picture
የእርቀ ሠላም ኮሚሽን አባላት እና ሰራተኞች የአረንጓዴ አሻራን መረሃ ግብር ከግብ ለማድረስ ዛሬ ጽ/ቤቱ እና በእንጦጦ አረንጓዴ ፓርክ ችግኝ ተከላ አካሂዷል፡፡
የኮሚሽኑ አባላት ከ የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን ጽ/ቤት ሠራተኞች እንዲሁም ከአዲስ አበባ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ጋር በመሆን በኮሚሽኑ ጽ/ቤት ቅጥር ግቢ እና በእንጦጦ አርንጓዴ ባርክ ችግኝ ተክለዋል፡፡
የኮሚሽኑ ዋና ሰብሳቢ ብፅዕ ካርዲናል ብርሃነ እየሱስ ሱራፊል የአረንጓዴ አሻራ ስኬት በአገሪቱ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ስለሚኖረው ሁሉም ሊተባበር ይገባል ብለዋል፡፡
Comments

የእርቀ ሠላም ኮሚሽን ከአዲስ አበባ፣ አምቦ፣ ወሎንኮሚና ሀዋሳ ከተማ የተውጣጡ በጐ ፈቃደኛ ወጣቶች በዕርቀ ሠላም ሃሳብ ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡

6/17/2020

Comments

 
Picture
የእርቀ ሠላም ኮሚሽን ከአዲስ አበባ፣ አምቦ፣ ወሎንኮሚና ሀዋሳ ከተማ የተውጣጡ በጐ ፈቃደኛ ወጣቶች እርስ በእርሳቸው እንዲተዋወቁ እና በዕርቀ ሠላም ሃሳብ ዙሪያ በጋራ በሚሠ\በት ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል፡፡
 
በውይይቱ ላይ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ ትብብር መሥራች ኦባንግ ሚቶ ወጣቶች ሰው በመሆናቸው ብቻ ከሌሎች ወጣቶች ጋር በጋራ የመቆም መንፈስ በሚያጎለብቱበት ሁኔታ ላይ የማነቃቂያ ንግግር አድርገዋል፡፡
 
የእርቀ ሠላም ኮሚሽን አባል አቶ ታም\ ለጋ ስለ እርቀ ሰላም ኮሚሽን ሚና፣ እስካሁን ስላካሄዱት ተግባር ወደፊት ስለሚሠ\ባቸው ተግባራት ገለፃ አድርገውላቸዋል፡፡
 
“ወጣት ለወጣት ለዕርቀ ሠላም” በሚል በበጐ ፈቃደኛ ወጣት ሄኖክ ባዮ ባዘጋጀው ወጣቶች ምን ማድረግ እንዳለባቸው በሚያስችል ፅሑፍ ላይ ተወያይተዋል፡፡​
Comments

ከአዲስ አበባ እና ኦሮሚያ የተወጣጡ በጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ለሐዋሳ ወጣቶች የኮቪድ - 19 መከላከያ የሚሆን የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን አበረከቱ፡፡

6/11/2020

Comments

 
Picture
ከአዲስ አበባ እና ኦሮሚያ /ኦሎንኮሚ እና አምቦ/ የተወጣጡ በጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ለሐዋሳ ወጣቶች የኮቪድ - 19 መከላከያ የሚሆን የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን አበረከቱ፡፡ 
“ወጣት ለወጣት” በሚል ሃሳብ ወደ ሐዋሳ የተንቀሳቀሱት ወጣቶች በከተማዋ በጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ደማቅ አቀባበል ተደርጐላቸዋል፡፡
በተጨማሪም በሚሊንየም አዳራሽ በጎ ፍቃደኛ ወጣቶች እስካሁን በየከተሞቻቸው ያከናወኑትንና ወደፊት ምን ሊያደርጉ እንዳሰቡ ውይይት አድርገዋል፡፡
“ችግር እንንቀል፤ ችግኝ እንትከል” በሚል እሳቤ በከተማው በሚገኘው ታቦር ተራራ ላይ በጋራ ችግኝ ተክለዋል፡፡ በጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ያደረጓቸው የመተሳሰብ እና የመደጋገፍ የቆየ ባህላችን መጠበቅና ወደፊትም ለሠላም ግንባታው ወጣቱ መሪ በመሆን የጎላ ድረሻ እንዲወጣ የኮሚሽኑ ሰብሳቢ ብፁዕ አቡነ ካርዲናል ብርሃነ እየሱስ አሳስበዋል፡፡
​ 
የዕርቀ ሠላም ኮሚሽን ወጣቶቹ ያካሄዱት የተቀደሠ ተግባር እንዲጠናከር ድጋፉን እንደሚቀጥል ገልፀዋል፡፡
Comments

‹‹ ወጣት ለወጣት ››

6/4/2020

Comments

 
​ከአዲስ አበባ እና ከኦሮሚያ ኦሎንኮሚና አምቦ ከተሞች የተወጣጡ ወጣቶች ‹‹ ወጣት ለወጣት ›› በሚል መርህ ለሐዋሳ ወጣቶች ኮቪድ 19 ለመከላከል የሚያስችሉ ቁሳቁሶችን ለማበርከትና ያለውን መልካም ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችል ጉዞ ጀምረዋል፡፡
ከአዲስ አበባ እርቀ ሰላም ኮሚሽን ጽ/ቤት ሲነሱም  በእርቀ ሰላም  ኮሚሽን ሰብሳቢ ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነየሱስ ሱራፌል እና ከኦሮሚያ በመጡ አባገዳ ገመዳ ሁንዴ አሸኘኘት ተደርጓል፡፡  
Comments

    Archives

    February 2021
    November 2020
    October 2020
    September 2020
    August 2020
    July 2020
    June 2020
    May 2020
    March 2020
    February 2020
    September 2019

    Categories

    All
    News

    RSS Feed

Picture
                          Social Media
                              Facebook : ERC
​
                              
Twitter : ERC

        © 2020 Ethiopian Reconciliation Commission​​
  • Home
  • News
    • Press Release
    • Press Conference
  • Event
  • Complaint Information
  • Videos
  • About
    • Members
    • Gallery
  • Contact